የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት በክረምት በጎ ፍቃድ እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል::
የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት በክረምት በጎ ፍቃድ መርሃ-ግብር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ሲገኝ በዛሬው ዕለትም በቁጥር ሁለት ዳዊት አረጋውያን መርጃ ማዕከል በመገኘት የችግኝ ተከላ እንዲሁም የምግብ ግብአት እና የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል። በመርሃ ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደረጀ ፀጋዬ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እና ተጠሪ ተቋማት በበጎ ፍቃድ አገልግሎት…


