የድሬዳዋ አሰተዳደር በወረዳ 01 እና 02 “ከቃል አስከ ባህል” በሚል መሪ ቃል በብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የተላለፉ ውሳኔዎችና እና አቅጣጫዎች ላይ ለነዎሪዎች የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ተካሄደ።
በአስተዳደሩ በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ ነዎሪዎች ከቃል እሰከ ባህል በሚል መሪቃል የሚያካሂዱት ውይይት በወረዳ 01 እና በወረዳ 02 የግንዛቤ መድረክ ውይይት ተደርጓል። በወረዳ 01 በተካሔደው ህዝባዊ ውይይት የተገባውን ቃል ለመፈጸም እና ነዋሪውን በታማኝነት ለማገልገል ውጤታማ ስራ ለመስራት በአስር ይዘቶች ተከፍለው የተዘጋጁትን የመወያያ ሰነዶች ከቃል እስከ ባህል ፣ ብሔራዊ ትርክትን ማፅናት፣ ውጤታማ የሠላም ግንባታ ለመሰራት የህዝብ ተግባቦት…


