ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ አዲስ ቅርንጫፉን በሃረማያ አስመረቀ
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ተደራሽነቱን በማስፋት በማያ ሲቲ በሃረማያ ከተማ አዲስ ቅርንጫፉን በዛሬው ዕለት አስመርቋል። ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ የፋይናንስ ተደራሽነቱንና አካታችነቱን በማጠናከር የተቋሙ ታላሚ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ማለትም መጠነኛ ገቢ ያላቸውና አነስተኛ ገቢ በሚያስገኙ ሥራዎች የተሰማሩትን ብሎም ወጣቶችና ሴቶችን በስፋት በሚሰጣቸው የብድርና ቁጠባ አገልግሎቶቹ እየደረሰ ይገኛል። ዛሬም የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት አዲስ ቅርንጫፉን በታሪካዊው የሃረማያ ሃይቅ…


