ታሪክ ከማይዘነጋው የመለዮ ለባሽ የአዲስ ምሩቃን፣ በተለይም በርከት ያሉ ሴት አየር ወለዶች የተመረቁበትን በዓል በጋራ በሀዋሳ ከተማ ለማክበር በመገናኘታችን የተሰማኝን ታላቅ ደስታ ልገልጽላችሁ እወዳለሁ።
“የእኛ ተልዕኮ ራዕይ ያለው ለትውልድ የሚሻገር ሁነኛ ተቋም መፍጠር ነው። የእኛ ተልዕኮ ውጊያ የሚያስቀር፣ ውጊያ የሚጨርስ Elite Force መገንባት ነው። የእናንተ ተልዕኮ ኢትዮጵያን መገንባት፣ ኢትዮጵያን መጠበቅ፣ ኢትዮጵያን ማጽናት እና ኢትዮጵያን ማሸጋገር ነው።” ኢትዮጵያ በልጆቿ ላብ ትሰራለች፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ አጥንት እና ደም ትጸናለች፤ ኢትዮጵያ አልተደፈረችም አትደፈርም፤ በክብር እና በነጻነት ለልጆቻችን የምናሸጋግራት ብቸኛዋ የአፍሪካ ፈርጥ ሆና ትቀጥላለች።…


