በድሬዳዋ አስተዳደር በዘንድሮው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ ከ5ሺ በላይ ሄክታር መሬት ማልማት ተችሏል::
በአስተዳደሩ”የተቀናጀ የበጋ ወራት የተፋሰስ ልማት ለግብርና ስኬት” በሚል መሪ ሀሳብ ሲካሄድ የነበረው የ2018 የተፋሰስ ልማት የመዝጊያ እና የእውቅና መርሃ ግብር ተካሂዷል። በመርሃግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጅሀር፤ አስተዳደሩ ለተፋሰስ ልማት ስራ ትኩረት በመስጠት ተፈጥሮን ወደነበረበት ለመመለስ ባከናወነው ተግባር ውጤት ማስመዝገቡንም ተናግረዋል። የተፋሰስ ልማት ስራዎች ሀገሪቱ የጀመረችውን ከተረጅነት የማላቀቅና ምርትና ምርታማነትን…


