ሁሉም የድሬዳዋ ወዳጆች ግብርን በአግባቡ በመክፈል እውነተኛ ተቆርቋሪነታቸውን በተግባር እንዲያሳዩ ጥሪ ቀረበ
“ግዴታዬን እወጣለሁ፣ መብቴንም እጠይቃለሁ” በሚል መሪ ቃል ከግንቦት 18-ሰኔ 16 ቀን 2011 ዓ.ም ለአንድ ወር በተለያዩ መርሃ ግብሮች የሚተገበር የታክስ ንቅናቄ በድሬዳዋ አስተዳደር ተጀመረ፡፡ የታክስ ንቅናቄው የመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይም በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ሚኒስቴር ዴታ የሆኑት አቶ መሐመድ አብዶ እና የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሐዲ ጊሪን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና የስራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች…


