በድሬዳዋ አስተዳደር ባለፉት 6 ወራት በህገ-ወጥ መልኩ ሊወጡና ሊገቡ የነበሩ ከ 1.7 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመቱ ምርቶች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ::
በድሬዳዋ አስተዳደር የንግድ፣ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት (የ6 ወራት) የፀረ ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ መከላከል፣ የኑሮ ውድነት መቀነስና ዋጋ ማረጋጋት እንዲሁም ኤክስፖርት ምርት ማሳደግ የጋራ ግብረ-ኃይል ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዛሬው ዕለት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በዚህም በመድረኩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ንግድ፣ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ባለፉት 6 ወራት…


