ድሬ ማይክሮ ፋይናስ የብድርና ቁጠባ ተቋም የአገልግሎት ተደራሽነቱን ለማስፋት ባንክ ተደራሽ የማያደርጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር 02 ወረዳ ሀሎሌ መንደር 8ኛ ቅርንጫፉን ከፍቶ አስመርቋል ።
በቅርንጫፉ የመክፈቻ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሐመድ እንደገለፁት ተቋሙ ባንክ ተደራሽ የማያደርጋቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችና ሴቶችን ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኝ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል ። ኃላፊዋ አያይዘውም ተቋሙ በዘርፉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ መስራት እንዳለበት አብራርተዋል ። የድሬ ማይክሮ ፋይናስ የብድርና ቁጠባ…


