ከ 38 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የድሬዳዋ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃና ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ህንፃ ተመረቀ፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር ልዩ ስሙ ከዚራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተገነባው የመጀመሪያ ደረጃና ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ህንፃ የተመረቀ ሲሆን በምረቃው ስነ-ስርዓቱ ላይም ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች፣ የሀይማኖት አባቶችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል፡፡ በአስተዳደሩ የተገነባው የመጀመሪያ ደረጃና ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ህንፃ የፍትህ ስርዓቱን ለማጎልበት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረውና ህንፃውም የተቋሙን አገልግሎት ምቹ ለማድረግ ይቻል…


