ማህበረሰቡ ሴቶች በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ተጠቃሚነታቸው ለማሳደግ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡
የአለም የሴቶች ቀን ማርች 8 ከየካቲት 21 ጀምሮ በተለያዩ ዝግጅቶች በአስተዳደራችን እየተከበረ ነው፡፡ ከእነዚህ ዝግጅቶች መካከል በአስተዳደሩ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ አዘጋጅነት “የሴቶችን መብት የሚያከብር ማህበረሰብ አንገንባ” በሚል መሪ ቃል ሴት አመራሮች የተሳተፉበት የቶክ ሾው መድረክ ተካሄደዋል፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ ለ110ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ45ኛ ጊዜ የሚከበረው የዘንድሮ የአለም ሴቶች ቀን በተለይም በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን…


