ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየዉ የድሬደዋዳደር የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ ተጠናቀቀ። በግምገማ መድረኩ የተለያዩ አስፈጻሚ አካላት የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡
ሰኔ 27/2014 ዓ.ም የተጀመረው የድሬዳዋ አስተዳደር የ2014 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ መድረክ በትላንትናው ውሎው የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ፣የፍትህ፣ፀጥታና ህግ ጉዳዮች ቢሮና የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የስራ አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡ ከተሳታፊዎች የተለያዩ አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ተሳታፊዎቹ ላነሷቸው ጥያቄዎችም ሪፖርት ያቀረቡት ተቋማት የስራ ሃላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በእለቱ የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ባቀረቡ ተቋማት…


