በድሬዳዋ አስተዳደር በኮሪደር ልማት የታደሰውና ለበርካታ ሺህ ዜጎች የኑሮ መሰረት የሆነው ታሪካዊው የቀፊራ የገበያ ማዕከል በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል።
በ1939 ዓ.ም አሁን ያለውን ቅርፅ ይዞ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የቀፊራ የገበያ ማዕከል፣ ለዘመናት ሲታይበት የነበረውን የፅዳት ጉድለት፣ የትራፊክ መጨናነቅና ህገ-ወጥ ንግድ ለመቅረፍ በሚያስችል መልኩ በኮሪደር ልማት ታድሶ ለምረቃ በቅቷል። ማዕከሉ በዘመናዊ መልኩ መታደሱ ለሸማቾችና ለነጋዴዎች ምቹ ሁኔታን ከመፍጠሩ ባለፈ፣ ለከተማዋ ኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል። የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ማዕከሉ…


