የገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን በገጠር ያለውን ጥሬ ሃብት ወደ ኢንደስትሪ በመቀየር ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለፀ
የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ፣ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ በመሆን በድሬዳዋ አስተዳደር የገጠር ኢንደስትሪያላይዜሽን ሁሉን አቀፍ ልማት ስተራቴጂካዊ እምቅ አቅም ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር አካሄደ። በመርሃ ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባ አደም የገጠር ኢንደስትራላይዜሽን በገጠር ያለውን ሰፊ የሰው ሃይል ወደ ስራ የሚያስገባ፣ ለስራ ፍለጋ የሚደረገውን ፍልሰት የሚቀንስ፤ የተመጣጠነ የገቢ ዕድገት እንዲኖር የሚያስችል እንዲሁም…


