በ 8 ተኛው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ላይ ነዋሪዎች ብሎም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በጋራ በመሆን መስራት እንደሚገባቸው ተገለፀ ።
የድሬዳዋ አስተዳደር የግብርና ውሀ ማእድንና ኢነርጂ ቢሮ 8 ተኛውን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎችን አስመልክቶ የክላስተርና የቀበሌ ደጋፊ አመራሮች ተሳታፊ የሆኑበት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል ። በግንዛቤ ማስጨበጫው ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ከድር ጁሀር ከዚህ ቀደም የተሰሩ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች አሁን ላይ ያሉበትን ደረጃ በየቀበሌ ከመገምገም…


