በአስተዳደሩ ያሉ ዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ጥረት እየተደረገ ይገኛል ሲሉ የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ስራ አስኪያጅ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ጀማል ኢብራሂም(ኢ/ር) ተናገሩ ።
የከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት እና ተጠሪ ተቆማት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተካሄደ ። በድሬዳዋ አስተዳደር የሴፍትኔት ተጠቃሚ የሆኑ ዜጎችን ማህበራዊ የኑሮ ደረጃቸውን ለማሻሻል የተጠቃሚዎችን የግል መረጃ በአግባቡ እያጣራን ፍታዊነትን ለማረጋገጥ ስራ መጀመሩን የከተማ ስራ አስኪያጅ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ኢንጂነር ጀማል ኢብራሂም ተናግረዋል ። በከተማ ስራአስኪያጅ ፅፈትቤት ስር የተጀመሩትን የሶስተኛው…


