መምህራን ለትዉልድ ቀረፃና ለሀገር ግንባታ ትልቅ ድርሻ እንዳላቸው ተገለፀ::
የድሬዳዋ መምህራን ማህበር የ2ኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና የ 37ኛው መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ ማካሄድ ጀምሯል። በዚህም በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የኢትዮጲያ መምህራን ማህበር ተወካይ ወ/ሮ ደብሪቱ ጌታቸው ማህበሩ የመምህራንን መብትና የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ ባለፈ በሀገራዊ ነባራዊ ጉዳዮች ላይ በስፋት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የማህበሩ አባላት ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ እንደሚገኝ የገለፁት ወ/ሮ ደብሪቱ ማህበሩ የእርስ በእርስ ትስስርን የማስፋት ስራ…


